ð. መጻጉዕ ፡- አራተኛው እሁድ መጻጉዕ ይባላል፡፡ መጻጉዕ ማለት በሽተኛ ማለት ነው ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕበራይስጥ ቤተ ሳይዳ ወደምትባል አንዲት መጠመቂያወርዶ በልዩል ደዌያት የተያዙ ብዙ ሕሙማንን መፈወሱ የሚወሳበት ፣ የሚዘመርበት ሳምንት ነው ፡፡
በተለይም ለሰላሳ ስምንት ዓመታት
በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ የነበረው አንድ ሕሙም በጌታ ቃል ተፈውሶ አልጋውን ተሸክሞ ወደ ቤቱ መሄዱ በቅዱስ መጽሓፍ በጉልህ
ተመዝግቧል ፡፡
ዮሐ. ñ ፥ í – õ
እኛም በለን አቅም በነፍስ በሥጋ
የተቸገሩትን ሁሉ መርዳትና ማገዝ እንደለብን የምንማርበት ሳምንት ነው ፡፡ ሕሙማንን መጠየቅ ፣ የተሰሩትን መገብኘትና ማስፈታት
፣ የተራቡትን ማጉረስ ፣ የተጠሙትን ማጠጣት ፣ የታረዙትን ማልበስ ያዘኑትን ማረጋጋት ከጌታችን የተማርናቸው ክርስቲያናዊ ተግባራት
ናቸው ፡፡
የቤተ ክርስቲያን ልማቷ (ፕሮጀክቷ) በሰው ልብ ላይ ነውና በተግባራችን ፣
በቀላችን ፣ በአኗኗራችን ለሰዎች ቀናውን መንገድ ማሳየትና በድከማቸው ሁሉ የሳምንቱ የማኅቶት መልእክት ነው ፡፡
የእለቱ መዝሙር ፡- አምላኩሰ ለአዳም
ምንባብ ፡- ገለ. 6
፥ 1
– õ ፤ ያዕ. 3 ፥ %ð – öô ፤ የሐዋ. 3 ፥ %2 -ö6
ምስባክ ፡- እግዚአብሔር ይረድዖ
ውስተ ዓራተ ሕማሙ ፡፡ ወይመይጥ ሎቱ ኩሎ ምስካቢሁ እምደዌሁ አንሰ እቤ እግዚኦ ተሰሐለኒ ፡፡ መዝ. ፵(፵í) ፥ 3 - ð
ወንጌል ፡- ማር. 2 ፥ í -ö2
No comments:
Post a Comment